==========================================

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን እየገነቡ ከሚገኙ ኮንትራክተሮችና አማካሪዎች ጋር ትምህርት ቤቶቹ ጥራታቸውን ጠብቀው በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ተገንብተው እንዲጠናቀቁ የሚያስችል ውይይት አካሂዷል፡፡

ውይይቱን የመሩት የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ መኳንንት አደመ በክልላችን እየተገነቡ የሚገኙ ሶስት አዳሪ ትምህርት ቤቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ማጠናቀቅ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማፍራት የሚያስችል በመሆኑ ኮንትራክተሮች በጥራትና በፍጥነት ስራቸውን ማከናወን እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

በሰቆጣ፣ ደብረታቦርና ፍኖተ ሰላም ከተሞች በሶስት ነጥብ ዘጠኝ ቢሊየን ብር በጀት እየተገነቡ የሚገኙ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የግንባታ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በውይይቱ የተገኙ የግንባታ ተቋራጮች ያጋጠሙ ችግሮችን በመፍታት በጥራትና በወቅቱ ገንብተው ለማስረከብ ቃል ገብተዋል፡፡

 

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ

  1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
  2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
  3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
  4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse

ያግኙን

  1. በቲክቶክ ገፃችን Amhara Education Bureau

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *