ለመሆኑ ከመምህራን ከተማሪዎች፣ ከትምህርት አመራሩና ባለሙያዎች በዚህ ወቅት ምን ይጠበቃል?

  1. ከሰኔ 28-02/11/2013 ዓ.ም የሚሰጠዉ የክፍል ፈተና ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፣  ሮስተር በወቅቱ እንዲሰራ ማድረግ፣  ዉጤት ትንተና መስራትና ለሚመለከተው ማድረስ፡፡
  2. ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች፣ የአካባቢው ማህበረሰብ የትምህርት አመራርና ባለሙያዎች የትምህርት ዘመኑ ከመጠናቀቁ በፊት ትምህርት ቤቶችን አረንጓዴ ሳቢና ማራኪ ለማድረግ  የአረንጓዴ ልማት የችግኝ ተከላ  በትምህርት ቤቶች መትከል፡፡
  3. መምህራን በሚያስተምሩበት የትምህርት ዓይነት ለሚቀጥለው የትምህርት ዘመን እንዲያቅዱ አቅጣጫ መስጠት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፡፡
  4. ሁሉም ትምህርት ቤቶች የትምህርት ቤት ማሻሻያ አቅድ ማቀድ መከታተል ይኖርባቸዋል፡፡ እቅዱ ልዩ ፍላጎትን እና ጾታን ያካተተ መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል፡፡
  5. ሁሉም ተማሪዎች በአመቱ መጀመሪያ ከትምህርት ቤት የተዋሱትን መማሪያ መጸሀፍት እንዲመልሱ ማድረግ፡፡
  6. በትምህርት ቤት ሊሰሩ የሚገቡ የክረምት ስራዎችን የትኩረት ነጥቦች በመለየት ማቀድና መተግበር፡፡
  7. የ2013 የትምህርት ዘመን የስራ አፈጻጸም ግምገማ በማድረግ ለ2014 የትምህርት ዘመን እቅድ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መንገድ ማቀድ፡፡
  8. መረጃዎችን አደራጂቶ መያዝ መተንተን፣  በግብዐትነት መጠቀም፣ ለሚመለከተዉ አካል ማሳወቅ፡፡

 

 

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *