ትምህርት ሚኒስቴር ከሮተሪ ኢንተርናሽናል ጋር በጋራ ለመስራት የመግባቢያ የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡
—————————————-
ትምህርት ሚኒስቴር ከሮተሪ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጋር በትምህርቱ ዘርፍ በጋራ ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡
የመግባቢያ ሰነዱ በንጹህ ውሃ አቅርቦትና በሌሎችም ትምህርት ነክ ጉዳዮች በጋራ ለመስራት እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ ር ኢንጅ) የተደረገው የመግባቢያ ስምምነት በትምህርት ቤቶች የሚስተዋለውን የውሃና ንጽህና አጠባበቅ ችግሮች ለመቅረፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
ስምምነቱም በሀገር አቀፍ ደረጃ በተቀናጀ መንገድ ስራዎችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመተግበር እንደሚያስችልም ገልፀዋል፡፡
የሮተሪ ኢትዮጵያ ሊቀመንበር ተሾመ ከበደ በበኩላቸው በትምህርት ቤቶች የውሃ አቅርቦቶች እንዲኖር የሚያሰችል ፕሮጀክት መዘጋጀቱን ገልፀው በአጭር ጊዜ ወደ ስራ ለመግባት ዝግጅቶች እያደረጉ እንዳለም ገልፀዋል፡፡
ሮተሪ ኢንተርናሽናል የተለያዩ ስራዎችን በትምህርት ዘርፉ እየሰራ የሚገኝ ተቋም ነው።
ዘገባው የትምህርት ሚኒስቴር ነው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ Amhara National Regional State Education Bureau
በዌብሳይት https://www.anrseb.gov.et/
በቴሌግራም https://t.me/anrse
ፌስቡክ https: Amhara Education Bureau