ሀንጋሪ ለኢትዬጵያ የምትሰጠውን የነፃ የትምህርት እድል አጠናክራ እንደምትቀጠል አስታወቀች።
——————————-
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የሀንጋሪ መንግስት አምባሳደር ክቡር አቲላ ቶማስ ጋር በነፃ የትምህርት ዕድል ዙሪያ ውይይት አደርገዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ(ፕ/ር) ከዚህ ቀደም የሀንጋሪ መንግስት ለኢትዬጵያዊያን ይሰጥ የነበረውን የነፃ የትምህርት ዕድል ስምምነት በማስቀጠል የሁለቱን አገራት ወዳጅነት ማጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
አምባሳደር ክቡር አቲላ ቶማስ በበኩላቸው አገራቸው በሁለተኛ ዲግሪ እና በሶስተኛ ዲግሪ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን ነፃ የትምህርት ዕድል ከዚህ ቀደሙ በተሻለ ሁኔታ ቁጥሩን በመጨመር እንደምትሰጥ ገልፀዋል፡፡
የነፃ የትምህርት እድሉ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት እንደሚያጠናክርም በውይይቱ ተነስቷል።
በየአመቱ የሀንጋሪ መንግስት ለኢትዬጵያ ተማሪዎች በሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ የነፃ ትምህርት እድል እንደምትሰጥ ይታወቃል።
መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው
በአሸባሪው የህወሓት ቡድንና ወራሪው የትግራይ ሃይል የተዘረፉና የወደሙ የትምህርት ተቋማትን መልሶ ለመገንባት እኔም የድርሻዬን እወጣለሁ!!!
ከአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያና የዌብ ሳይት አማራጮች ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጠቀሙ ::
ፌስቡክ Amhara-Education-Bureau
ዩቱዩብ UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
በዌብሳይት https://www.anrseb.gov.et/
በቴሌግራም https://t.me/anrse

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *