የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ከወሎ ቀጠና የትምህርት አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር የዘጠኝ ወር ስራ አፈፃፀም ግምገማውን ከሚያዝያ 22_23/2017ዓ.ም በደሴ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ ማጠቃለያም በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ሙሉነሽ ደሴ መልዕክት አስተላልፈዋል። ሙሉ መልዕክቱም እንደሚከተለው ቀርቧል።
*****************
✅ የትምህርት መዋቅሩ ባሳለፍናቸው ወራቶች ተሳትፎን በማረጋገጥ ረገድ ችግሮች ቢገጥሙትም ተማሪዎችን በማብቃት በኩል ግን ተሰፋ የሚሰጡ ሥራዎች ተሰርተዋል።
✅ ከክልል እስከ ትምህርት ቤት ድረስ እየተደረጉ ያሉ የድጋፍና ክትትል ሥራዎች አበረታች እንደሆኑ ተገልፆል።
✅ የት /ት ሸፋኑ አለመሳካቱ. በትውልዱ ላይ የሚፈጥረውን ክፍተት ተረድተን ሕብረተሰቡ ትምህርትን ቀዳሚ አጀንዳው አድርጎ እንዲሰራ እርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
✅ ትምህርት ከየትኛውም ፖለቲካ ነፃ ነው። ትምህርት የየትኛውም ፖለቲካ ማስፈፀሚያ አጀንዳ መሆን የለበትም። ሊሆንም አይገባም። ይህንን ማህበረሰቡ ተረድቶ ከትምህርት ገበታ የራቁ ልጆቹ ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ያለ መሠልቸት መስራት ይገባል ብለዋል።
✅ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል፣ በአሁናዊ የሰላም ችግሮች ጉዳት የደረሰባቸውን የትምህርት ተቋማት መልሶ መገንባት፣ ግብአት ማሰባሰብ በተለይ አልማ የሚሰራቸው ሥራዎች ብዙዎቹ የትምህርት በመሆናቸው ለአልማ ስራ ስኬት ሁላችንም ድጋፍ ልናደርግ እንሚገባ አሳስበዋል።
✅ ወጣቱ ትውልድ ቴክኖሎጅ እንዲጠቀም፣ በዚህም ስራ ፈጣሪ እንዲሆን በትምህርት ቤቶች የተጀመረውን ኢትዮ_ኮደርስ ስልጠና በትኩረት መከታተል ይገባል።
✅ በቀሪ ወራት ሁሉንም ተማሪዎች ማብቃት ፤ በተለይ ክልል አቀፍና አገር አቀፍ ፈተና ላይ የሚቀመጡ የ6ኛ፣ 8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማብቃት የድጋፍ ስራዎችን ማጠናከር፣
✅ ግንባታዎች በተያዘላቸው ጊዜ መሠረት እንዲጠናቀቁ ክትትል ማድረግ፣
✅ ለ2018 የትምህርት ዘመን አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ከወዲሁ ማጠናቀቅ፣
✅ የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄን ማስቀጠል፣
✅ የህዝብ ግንኙነት ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ዶ/ር ሙሉነሽ በማጠቃለያቸው አንስተዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *