በአማራ ክልል የ2017ዓ.ም 6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ‼️
*********
ሐምሌ 27/2017(ትምህርት ቢሮ) በአማራ ክልል በ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በቴክኖሎጅ በመታገዝ እርማቱ ተካሂዶ ውጤቱ ይፋ ሆኗል።
ተማሪዎችም ውጤታችሁን ከታች በተቀመጡ ሁለት አማራጮች ማየት የምትችሉ ሲሆን፤
➊ በኮምፒውተር ወይም ስልካችሁ ባለዉ የድር መፈለጊያ መተግበሪያ ( Web browser Application ) ላይ
1) 👉 ለ6ኛ ክፍል ተፈታኞች https://amhara6.ministry.et/#/result የሚለውን አድራሻ በመፃፍ
2)👉 በሚመጣው ቅጽ(form) ላይ
የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number) እና የመጀመሪያ ስም (First name) በማስገባት
3)👉ዉጤት ይመልከቱ (Check your result) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ማየት ይችላሉ፡፡
❷ በተጨማሪም @emacs_ministry_result_qmt_bot 👉 በሚለው የቴሌግራም ቦት ላይ በመግባት ተማሪዎች ውጤታቸውን መመልከት የሚችሉ ሲሆን ለመጀመሪያ
👉start የሚለውን ይጫኑ!
👉በመቀጠልም ክፍልዎን ይምረጡ
👉ከዚያም ክልልዎን ይምረጡ
👉በመቀጠል የምዝገባ መለያ ቁጥር እና የመጀመሪያ ስምን በማስገባት ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ።
ተማሪዎች ማንኛውም ከውጤት ጋር የተያያዘ ቅሬታ ካላቸው ማቅረብ ይችላሉ። ቅሬታቸውንም ለማቅረብ
➌በኮምፒውተር ወይም ስልካቸው ላይ ባለዉ የድር መፈለጊያ መተግበሪያ ( Web browser Application ) ላይ
1) 👉 ለ6ኛ ክፍል ተፈታኞች https://amhara6.ministry.et/#/complaint የሚለውን አድራሻ በመፃፍ
2)👉 በሚመጣው ቅጽ(form) ላይ
የተማሪውን መለያ ቁጥር (Registration Number)እና
የተማሪውን የመጀመሪያ ስም (First Name)በማስገባት
3)👉 የትምህርት ዓይነት አሳይ(Fetch course) የሚለውን ቁልፍ በመጫን
4)👉 ቅሬታ ማቅረብ የሚፈልጉበትን ይምረጡ
5)👉በመጨረሻም ሪፖርት (Add Complaint) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ቅሬታቸውን ማቅረብ ይችላሉ።
🎯 ማስታወሻ ፡ በቅድሚያ ቪፒኤን ማጥፋት ይኖርባችኋል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *